በዓለም ላይ ከሚገኙት ወደ 3000 የሚጠጉ የእባብ ዝርያዎች 600 የሚሆኑት መርዛማ ናቸው፤ የተነደፍነው በመርዛማ እባቦች መሆኑን እንዴት እንለያለን? ምንስ ማድረግ አለብን?
በዓለም ላይ ከሚገኙት ወደ 3000 የሚጠጉ የእባብ ዝርያዎች 600 የሚሆኑት መርዛማ ናቸው፤ 200 የሚሆኑት ደግሞ ለህክምና ወይም ለመድኃኒት አግልግሎት የሚጠቅሙ ናቸው፡፡ መርዛማ እባቦችን ለመለየት ይሄ ነው የሚባል መንገድ ለመከተል ይከብዳል፤ ምክንያቱም አብዛኛዎቹ የመለያ መንገዶች የቅርብ ምልከታን የሚፈልጉ በመሆኑ ነው፤ ስለዚህ ከእባቦች ስጋትና ጥቃት ነፃ ልንሆን የምንችለው ከእነርሱ በመራቅ ነው፡፡ የአንድ መርዛማ እባብ ንድፊያ የተለያዩ የሰውነት አካላት ላይ በፍጥነት ጉዳት ማድረስ ይጀምራል፤ እንደ ሳንባ፣ ልብ፣ የማዕከላዊ ነርቭ ስርዓት፣ የቀይ ደም ሕዋሶችና የጡንቻ ስርዓት ያሉት በቀጥታ ጉዳት ከሚገጥማቸው የሰውነት አካላት ውስጥ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በመሆኑም የእባብ መርዝ የነርቭ ስርዓትን የሚያጠቃ(neurotoxic)፣ በደም ሕዋሶች ላይ ጉዳት የሚያደርስ(haemotoxic)፣ ልብን የሚጎዳ(cardiotoxic) እና በጡንቻዎች ላይ እንከን የሚፈጥር(myotoxic) ተብሎ ሊከፈል ይችላል፤ በዚህ ምክንያት የሚሰጠውም የማርከሻ ሕክምና የተለያየ ነው፤ ይህ በመሆኑም በሕክምናው ስኬታማ ለመሆን በምን ዓይነት እባብ እንደተነደፍን ማወቅ አለብን፡፡ በዓለማችን ላይ በአመት ወደ 5 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በእባብ ይነደፋሉ፤ ከነዚህ ውስጥ ደግሞ 100 ሺህ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጣሉ በዓለማችን ላይ በአመት ወደ 5 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በእባብ ይነደፋሉ፤ ከነዚህ ውስጥ ደግሞ 100 ሺህ የሚሆኑት ህይወታቸውን ያጣሉ፤ 5 መቶ ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ቋሚ የአካል ጉዳት ይገጥማቸዋል፤ የመርዛማ እባብ ንድፊያ ማርከሻውን ካላገኘ ለሞት የመዳረግ ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ እባቦች በአማካኝ በሳምንት አንድ ጊዜ ይመገባሉ፤ ከተመገቡ በኋላ እንዲሁም ቆዳቸውን በሚሸልቱበት ጊዜ...
Comments
Post a Comment